የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበር "በሁለንተናዊው የተጠናከረ ማህበር ለሁለንተናዊ የመምህራን እና ከተማችን እድገት" በሚል መሪ ቃል ለሁለት ቀናት ባካሄደው 23ኛ መደበኛ ጉባኤ ማጠቃለያ ማህበሩ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክብርት ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ፣ ለትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ፣ ማህበሩን ላለፉት አምስት አመታት በፕሬዘዳንትነት ለመሩት አቶ ድንቃለም ቶሎሳ እና በየደረጃው ለሚገኙ የማህበሩ አመራሮች፣ በአመቱ ውጤታማ አፈጻጸም ላስመዘገበ የልደታ ክፍለ ከተማ ህዳሴ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህር ሾማ አብዲሳ እንዲሁም ከማህበሩ ጋር በአጋርነት በመስራት ውጤታማ ለሆኑ ተቋማት ዕውቅና ከመሰጠቱ ባሻገር ማህበሩን ለቀጣይ አራት አመታት የሚመሩ ስራ አስፈጻሚዎች ምርጫ ተካሂዷል።


.